የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአጋሮ ከተማ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ይበልጥ ምቹ አድርጓል

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ጅማ፤ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ) ፡- የአጋሮ የኮሪደር ልማት የከተማውን መልካም ገጽታ ከማጉላት ባለፈ ከተማዋን ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ይበልጥ ምቹ በማድረግ ለውጥ ማምጣቱ ተገለጸ።

የከተማው የኮሪደር ልማት 12 ነጥብ 4 ኪሎሜትር በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የከተማው አስተዳደር አስታውቋል።


ከአጋሮ ነዋሪዎች መካከል አቶ ሀፊዝ ከድር በሰጡት አስተያየት፤ የኮሪደር ልማቱ እግረኛና ተሽከርካሪ በተጨናነቀ ሁኔታ የሚጓዝበት የነበረውን ሂደት በመቀየር ይበልጥ ምቹ ማድረጉን ተናግረዋል።


ልማቱ የአጋሮን ከተማ መልካም ገጽታ በማጉላት ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከቀድሞ በተሻለ ምቹ በመሆን ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።

ሌላው የከተማዋ ነዋሪ መምህር ሲሳይ ማረጌ አጋሮ ፤ በኮሪደር ልማቱ መንገድን ከማስፋት ባሻገር የእግረኛ መንገድ መለየቱና አካፋይ መተላላፊያ ላይ የተተከሉት ችግኞች አረንጓዴን በማልበስ ጭምር የከተማዋን ውበት ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ ማስቻሉን ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹና ማራኪ ከማድረጉ ባለፈ ለበርካታ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ አቶ ነቢል አሊ ናቸው።

የተተከሉ ሳሮች እና የተገነቡ ፋውንቴኖች ለአጋሮ ከተማ ልዩ ውበት መሆኑንና ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚደግፉ ተናግረዋል።


የአጋሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ነዚፍ መሀመድአሚን በበኩላቸው፤ የከተማው የኮሪደር ልማት 12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።


ልማቱ የአረንጓዴ ልማት፣ ፋዎንቴኖችና ኮፊ ኮርነሮች የተካተቱበት ነው ያሉት ከንቲባው ከ10ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026