የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው- አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ሐይቅ ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ) ፡-በሐይቅ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አስታወቁ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልልና የደቡብ ወሎ ዞን አመራሮች የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።


በዚህ ወቅት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ፤ ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተመለከትነው የኮሪደር ልማት ጅምር ስራ የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ገጽታ ይበልጥ ውብ በማደረግ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኚዎችና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።

የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድና በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ሎጎ ፕሮጀክት የከተማዋን እድገት በማፋጠን የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።

መንግስት ከሕዝብ ጋር ተቀናጅቶ ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎቸንም የልማት ተግባራት እያከናወነ በውጤታማነት በመቀጠል የብልፅግናን ጉዞ እያሳካ መሆኑን አስረድተዋል።


የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በበኩላቸው፤ በዞኑ ስር በሚገኙ ሶስት ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው ብለዋል።


የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማስፈፀም ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የከተማውን የኮሪደር ልማት ሥራ እስከ ታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሀመድ ናቸው።


ልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገድን እንዲሁም አረንጓዴ ሥፍራና መዝናኛዎችንም ያካተተ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025