ሐይቅ ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ) ፡-በሐይቅ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አስታወቁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልልና የደቡብ ወሎ ዞን አመራሮች የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።
በዚህ ወቅት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ፤ ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተመለከትነው የኮሪደር ልማት ጅምር ስራ የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ገጽታ ይበልጥ ውብ በማደረግ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኚዎችና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።
የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድና በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ሎጎ ፕሮጀክት የከተማዋን እድገት በማፋጠን የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
መንግስት ከሕዝብ ጋር ተቀናጅቶ ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎቸንም የልማት ተግባራት እያከናወነ በውጤታማነት በመቀጠል የብልፅግናን ጉዞ እያሳካ መሆኑን አስረድተዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በበኩላቸው፤ በዞኑ ስር በሚገኙ ሶስት ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማስፈፀም ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማውን የኮሪደር ልማት ሥራ እስከ ታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሀመድ ናቸው።
ልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገድን እንዲሁም አረንጓዴ ሥፍራና መዝናኛዎችንም ያካተተ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025