
ሐይቅ ፤ ሰኔ 28/2017(ኢዜአ) ፡-በሐይቅ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ሲሉ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አስታወቁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልልና የደቡብ ወሎ ዞን አመራሮች የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።

በዚህ ወቅት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ፤ ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተመለከትነው የኮሪደር ልማት ጅምር ስራ የማንሰራራት ጉዞ ሂደቱን የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ገጽታ ይበልጥ ውብ በማደረግ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኚዎችና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል።
የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድና በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ሎጎ ፕሮጀክት የከተማዋን እድገት በማፋጠን የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
መንግስት ከሕዝብ ጋር ተቀናጅቶ ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎቸንም የልማት ተግባራት እያከናወነ በውጤታማነት በመቀጠል የብልፅግናን ጉዞ እያሳካ መሆኑን አስረድተዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በበኩላቸው፤ በዞኑ ስር በሚገኙ ሶስት ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የሐይቅ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማስፈፀም ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማውን የኮሪደር ልማት ሥራ እስከ ታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሀመድ ናቸው።

ልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገድን እንዲሁም አረንጓዴ ሥፍራና መዝናኛዎችንም ያካተተ ነው ብለዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026