አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በአሁኑ ወቅት 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሔደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ መንግስት የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመፍታት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።
የቤት ችግር ከፍተኛ ሥራ የሚፈልግ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ በመንግስት፣ በግል፣ በመንግስትና የግል ትብብር የመኖሪያ ቤቶቹ ግንባታዎች እየተካሄዱ መሆኑን አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅትም 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው፤ መንግስት ከግል ባለሃብቱ ጋር በቅንጅት በመስራት የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት አንድ ሚሊዮን ያህል ቤቶች መገንባታቸውን አውስተው፤ የመኖሪያ ቤቱ ግንባታ ደረጃውን የጠበቀና ለኑሮ ምቹ የሆነ በማድረግ ረገድ ሰፊ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከመኖሪያ ቤት ግንባታው ጎን ለጎንም ከ100 ሺህ ያላነሱ የመኖሪያ ቤቶች በክረምት በጎ ፈቃድ ጥገና የሚደረግላቸው መሆኑንም ነው ያነሱት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025