
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በአሁኑ ወቅት 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሔደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ መንግስት የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመፍታት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።
የቤት ችግር ከፍተኛ ሥራ የሚፈልግ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ በመንግስት፣ በግል፣ በመንግስትና የግል ትብብር የመኖሪያ ቤቶቹ ግንባታዎች እየተካሄዱ መሆኑን አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅትም 265 ሺህ ገደማ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመው፤ መንግስት ከግል ባለሃብቱ ጋር በቅንጅት በመስራት የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት አንድ ሚሊዮን ያህል ቤቶች መገንባታቸውን አውስተው፤ የመኖሪያ ቤቱ ግንባታ ደረጃውን የጠበቀና ለኑሮ ምቹ የሆነ በማድረግ ረገድ ሰፊ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከመኖሪያ ቤት ግንባታው ጎን ለጎንም ከ100 ሺህ ያላነሱ የመኖሪያ ቤቶች በክረምት በጎ ፈቃድ ጥገና የሚደረግላቸው መሆኑንም ነው ያነሱት።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026