የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ከ18 ማዞሪያ በአሸዋ ሜዳ እስከ ኬላ እየተገነባ ያለው ከ14 ኪሎሜትር በላይ የመንገድ ፕሮጀክት እየተፋጠነ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ ከ18 ማዞሪያ - አሸዋ ሜዳ - ኬላ መንገድ ባለው መስመር እየተከናወነ የሚገኘው ከ14 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ፕሮጀክት እየተፋጠነ መሆኑን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የመንገድ ፕሮጀክቱ የአዲስ አበባ - አምቦ - ነቀምት መስመር አካል ሲሆን፥ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ዕድገት ታሳቢ በማድረግ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ እየተሰራ መሆኑን አስተዳደሩ ገልጿል።

ኢዜአ የመንገድ ፕሮጀክቱን የግንባታ ሥራ ቅኝት በማድረግ የፕሮጀክቱን ኃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን አነጋግሯል።

በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የፕሮጀክት አስተባባሪ ኢንጂነር ዮሀንስ ሲሳይ እንደገለጹት፥ ፕሮጀክቱ 14 ነጥብ 72 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፥ በተጀመረ በሶስት ወራት ውስጥ የግንባታ ሂደቱ 20 በመቶ ደርሷል።


የመንገድ ግንባታው በጥቂት ጊዜ ውስጥ ትላልቅ የሚባሉ ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑን አንስተው በዚህ ዓመት መጨረሻ ድረስ የአስፋልት ማንጠፍ ስራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል፡።

መንገዱ የከተሞችን ዕድገት፣ የማህበረሰቡን ዘመናዊ አኗኗር ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተገነባ የሚገኝ ስማርት የመንገድ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ ስፋቱ 66 ሜትር ሲሆን ከዚህ ውስጥ የአስፋልት መንገዱ ስፋት 50 ሜትር መሆኑን ጠቅሰው፥ የእግረኛ፣ የብስክሌት፣ የመሮጫ መም እና አረንጓዴ ስፍራዎችን ማካተቱንም ገልጸዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የተሽከርካሪ ፍሰት ባለበት፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሚደረግበት አካባቢ እየተገነባ በመሆኑ በአፋጣኝ ለማጠናቀቅ ቀን ከሌሊት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የትራፊክ ፍሰቱን ከማሳለጥ በተጨማሪ በርካታ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ይዞ እንደሚመጣም ገልጸዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ ኢንጂነር ተካልኝ አስራት በበኩላቸው መንገዱ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን ከፍተኛ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

የምርት እንቅስቃሴን በፍጥነት ወደ ገበያ ተደራሽ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ በርካታ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ ማሳለፍ የሚያስችልና ለሀገር አቀራጭ መንገዶች መጋቢ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።


ከዲዛይን አንጻር ከፍተኛ የሚባለውን ደረጃ ያሟላ መሆኑን ገልጸው፥ በሦስት ደረጃ የአስፋልት ንጣፍ እንደሚሰራለት ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በሁለት ሀገር በቀል ተቋራጮች እየተገነባ መሆኑን አንስተው ይህም የሀገራችን የግንባታ ተቋራጮች ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በአግባቡ የመፈጸም ትልቅ አቅም እንዳላቸው ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ከ18 ማዞሪያ እስከ ኬላ ያለው መንገድ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት በመሆኑ ካሰቡት ለመድረስ ረጅም ጊዜን የሚጠይቅ እንደነበር ያነሱት በአካባቢው ሲያሽከረክሩ ያገኘናቸው ሙሉጌታ ጉልማ እና ጌታቸው ቢያድግ ናቸው።



አዲሱ የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ የትራፊክ እንቅስቃሴውን በማሳለጥ አሽከርካሪዎች በቀላሉና በአጭር ጊዜ የፈለጉበት ቦታ እንዲደርሱ በማገዝ እፎይታን ይሰጣል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026