የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የጤፍ ምርት እና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ) የጤፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ እሴት በመጨመር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።

በጤፍ ሰብል ልማትና እሴት ጨምሮ ማምረት ላይ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።

በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ለኢዜአ እንደገለጹት በኢትዮጵያ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች በጤፍ ልማት ላይ ተሰማርተዋል።

እነዚህን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ የጤፍን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ እሴት ጨምሮ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ጤፍን የኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርት ለማድረግ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ኢሳያስ፤ "የጤፍ ምርታማነት አናሳ መሆን፣ የምርጥ ዘርና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክፍተት የዘርፉ ማነቆዎች ናቸው ብለዋል።

በዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ረዳት ተወካይ ወርክቾ ጃተኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በጤፍ ልማት ላይ የጥናትና ምርምር ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

በጤፍ ምርትና ምርታማነት ላይ የሚደረግ ምርምር በሚፈለገው ደረጃ ያለመሆንና ጤፍን በሜካናይዜሽን ግብርና ለማልማት የማሽነሪዎች እጥረት መኖር በጥናት መለየቱን ገልጸዋል።


"የአንድ ሀገር ተቀዳሚ ምርት" የሚል ፕሮጀክት በመቅረጽ በጤፍ ምርት ላይ የምርምርና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የጤፍ ሰብል ከፍተኛ ተመራማሪ ሀብቴ ጁፋር (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የጤፍ ምርትና ምርታማነት ማነቆዎችን ለመፍታት ከግብርና ሚኒስቴርና ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል።


በዚህም በጤፍ ዝርያ ማሻሻል፣ በተመራማሪዎች አቅም ግንባታ እንዲሁም በጤፍ ምርትና ምርታማነት የባለድርሻ አካላት ፕላት ፎርምን ጭምር በማዘጋጀት እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026