አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ባለፉት ወራት 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎትን በኦንላይን ማከናወኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
70ሺህ አዳዲስ የንግድ ፈቃዶችን በኦንላይን መስጠቱን ቢሮው ገልጿል።
የንግድ ቢሮው ምክትል ኃላፊ ፍስሀ ጥበቡ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በበጀት ዓመቱ ለንግዱ ማህበረሰብ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የሚያሳልጡ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ጥቅም ላይ ማዋል ተችሏል ብለዋል።
በወረዳና በክፍለ ከተማ በተበታተነ መልኩ የሚሰጠውን የንግድ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት የሚያስችል አደረጃጀት ለመፍጠር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት 411ሺህ የንግድ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ በአሥር ወራት ብቻ 364ሺህ የንግድ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በኦንላይን መከናወኑን ተናግረዋል።
ከ70ሺህ የማያንሱ አዳዲስ የንግድ ፈቃድ ምዝገባ አገልግሎት በኦንላይን መሰጠቱንም ነው ጨምረው የገለጹት።
ህገ-ወጥና ኢ-መደበኛ የንግድ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መልክ ለማስያዝ ስኬታማ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ከሚወሰዱ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ባሻገር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ዘመናዊ የንግድ መስሪያ ቦታ በማዘጋጀት ወደ ህጋዊ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኦንላይን ንግድ ፈቃድ ካደሱ ነጋዴዎች መካከል አቶ ፍስሃ ገብረመስቀል፥ ቀድም ሲል የነበረው የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ እንዳልነበር በማስታወስ፥ አሁን ሁሉም ነገር ቀላል መሆኑን ተናግረዋል።
የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ንግድ ፈቃዳቸውን ማሳደስ በመቻላቸው ጊዜያቸውን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልት እንዳስቀረላቸው ጠቅሰዋል።
አዲስ የንግድ ፈቃድ ማውጣትም ሆነ የእድሳት አገልግሎትን በዘመናዊ መንገድ መጀመሩ ጊዜውን የዋጀ እና ለህብረተሰቡም ፋይዳው የላቀ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ አቶ ይርዳው ምትኩ ናቸው።
ሌላኛዋ አስተያያት ሰጪ ወይዘሮ መቅድስ ታደሰ፤ ቀድም ሲል ንግድ ፈቃድ ለማደስ ረጅም ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ላይ በኦንላይን መደረጉ ተጠቃሚ አድርጎኛል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025