አፋር፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) የአፋር ክልልን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን የክልሉ ውሃ እና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ።
በአፋር ክልል ቂልበት ረሱ ዞን መጋሌ ወረዳ ገሚሪዳ ቀበሌ በ38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በምረቃ ሰነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ አህመድ ሻሚ እንደገለፁት የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ናቸው።
በዛሬው ዕለት የተመረቀው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም ለህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሰጠና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በፀሐይ ብርሃን ኃይል የሚንቀሳቀሰውና 38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ከ5 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው በስፍራው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ማህበረሰቡ ላለፉት ዓመታት በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ሳቢያ ሲያጋጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ ተናግረዋል።
በተለይም እናቶች የመጠጥ ውሃ ለማግኘት ከሚያደርጉት ረጅም ጉዞ እንግልትና በዚህም ምክንያት ሲባክን የነበረውን ጊዜ በመቆጠብ ረገድ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል።
በምረቃ ስነ ሰርዓቱ ላይም የዞኑና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025