
አፋር፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) የአፋር ክልልን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን የክልሉ ውሃ እና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ።
በአፋር ክልል ቂልበት ረሱ ዞን መጋሌ ወረዳ ገሚሪዳ ቀበሌ በ38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በምረቃ ሰነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ አህመድ ሻሚ እንደገለፁት የክልሉን የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ናቸው።

በዛሬው ዕለት የተመረቀው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም ለህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሰጠና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
በፀሐይ ብርሃን ኃይል የሚንቀሳቀሰውና 38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ከ5 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልፀዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሐሰን በበኩላቸው በስፍራው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ማህበረሰቡ ላለፉት ዓመታት በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ሳቢያ ሲያጋጥመው የነበረውን ችግር እንደሚፈታ ተናግረዋል።


በተለይም እናቶች የመጠጥ ውሃ ለማግኘት ከሚያደርጉት ረጅም ጉዞ እንግልትና በዚህም ምክንያት ሲባክን የነበረውን ጊዜ በመቆጠብ ረገድ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል።
በምረቃ ስነ ሰርዓቱ ላይም የዞኑና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026