
ሮቤ ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፡-በባሌ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ257 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል ዘሮች መልማቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በባሌ ዞን የበልግ እርሻ ወቅት ከመጋቢት አጋማሽ እስከ ነሐሴ ያለውን ጊዜ የሚያጠቃልል መሆኑ ይታወቃል።
በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ደረጀ ግርማ እንዳሉት፣ በዞኑ በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ257 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል ዘሮች ለምቷል።
በዞኑ ከለማው የእርሻ መሬት መካከል ከ70 በመቶ የሚበልጠው የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ በኩታ ገጠም የለማ መሆኑንም አመልክተዋል።

አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ለማረጋገጥ ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ የሀገር ውስጥና የውጪ ገበያ አማራጮችን ጭምር ታሳቢ በማድረግ እንዲያመርት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በበልጉ ወቅት እየለማ ከሚገኘው አጠቃላይ መሬት መካከል ከ40 ሺህ ሄክታር የሚበልጠው ገበያ ተኮር በሆኑ ሰሊጥ፣ ማሾ፣ ቦሎቄና የለውዝ ምርቶች መልማቱን በማሳያነት አንስተዋል።
የዘንድሮ የዝናብ ስርጭት በተለይም በቆላማ አካባቢዎች ጥሩ ስርጭት ስለነበረው ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ መሆኑንና በአርሶ አደሩ እንክብካቤ እየተደረገለት እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ከዋና ዋና ሰብል ልማቱም 8 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ግብ መቀመጡንም ባለሙያው ተናግረዋል።
በዞኑ የሲናና ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙአውያ ፉዓድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በወረዳው በዘንድሮ የበልግ ወቅት 50ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ፣ ገብስና ሌሎች ሰብሎች ለምቷል።

በተለይም በዘንድሮው የበልግ አዝመራ የአርሶ አደሩን የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ይበልጥ ለማሻሻል በተቀመጠው ግብ መሰረት ከአጠቃላይ ልማቱ 60 በመቶ የሚበልጠው መሬት የተሻሻሉ አሰራሮችን በመጠቀም በኩታ ገጠም መልማቱን ተናግረዋል።
በልማቱ እየተሳተፉ ከሚገኙ የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ሐሰን አህመድ በሰጡት አስተያየት፣ በባለፈው የመኽር እርሻ ከአንድ ሄክታር መሬት ከ60 ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት መሰብሰባቸውን ተናግረዋል።
በዘንድሮ የበልግ ወቅት የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን በመጠቀም የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችል የሰብል እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውንም አክለዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026