የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የቢዝነስ ዲፕሎማሲ ለማጠናከር ቁርጠኛ ነች - አምባሳደር ትሮይ ፊትረል

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦ አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የቢዝነስ ዲፕሎማሲ በአዲሱ የትራምፕ አስተዳደር ዘመን ይበልጥ ለማጠናከር እንደምትሰራ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ቢሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ አምባሳደር ትሮይ ፊትለር ገለጹ።

አምባሳደር ትሮይ ፊትለር በአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ሀገራቸው ከአፍሪካ ጋር ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ትሰራለች ብለዋል።


በቅርቡም አሜሪካ አፍሪካን በተመለከተ የምትከተለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የቢዝነስ ዲፕሎማሲን መሰረት እንዲያደርግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአፍሪካ የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች በዛው ልክ እየተንቀሰቀሱ መሆኑን አንስተዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የአሰራር ማሻሻያዎች እስከ ማድረግ የሚደርስ ውሳኔ መተላለፉን ጠቅሰዋል።

ጎን ለጎንም በንግዱ ዘርፍ በሁለቱም ወገኖች መካከል ያሉ ተዋንያኖችን ተጠቃሚ ለማድረግ በማሰብ የጋራ ገበያው ምን አይነት ለውጥ ያስፈልገዋል በሚል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በተለይም የንግድ ትስስሩን ለማጠናከር ከዚህ በኋላ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ወደ አፍሪካ በሚያደርጉት ጉዞ አብረዋቸው የቢዝነስ ተወካዮች በጣምራ እንዲላኩና የተለያዩ የንግድና ኢንቨስትመንት ድርድሮች እንዲያደርጉ ይደረጋልም ነው ያሉት።

በሌላ በኩል አሜሪካ በአፍሪካ በቢዝነስ ዲፕሎማሲ ማዕቀፍ በሚኖራት ተሳትፎ በተለይም በዋና ዋና የመሰረተ ልማት ግንባታ ከምታደርገው ተሳትፎ በዘለለ በዲጂታል መሰረተ ልማት ማስፋፋት ላይ ይበልጥ እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።

ይህም አፍሪካ በዘመናዊው የዓለም የንግድ ሥርዓት ውስጥ ውጤታማ ተሳትፎ እንዲኖራት ያስችላል ብለዋል።

በጥቅሉ የአሜሪካ የንግድና ኢንቨስትመንት ሥራ ለአፍሪካ በእጅጉ ይጠቅማል ያሉት አምባሳደር ትሮይ፤ ይህ የአሜሪካ የቢዝነስ ሥራ በአመዛኙ በአዳዲስ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ሥራ ላይ የሚያተኩር መሆኑን መናገራቸውን የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026