
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በክረምቱ ወቅት የፍራፍሬ ችግኝ በ5 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቡናና ሻይ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒ አሚን እንዳሉት በዘንድሮ የክረምት ወቅት በተለይ በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ተክሎችን ለማልማት ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።
ለዚህም የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ምርጥ ዘር በማባዛት በልዩ ሁኔታ በኩታ ገጠም ለማልማት በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በአጠቃላይ በክረምቱ 200 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለማልማት መታቀዱን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 5 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሚለማው መሬት 500 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ገልጸው ልማቱም በሰባት ዞኖች ውስጥ በሰፊው እንደሚከናወን ተናግረዋል።
በክረምቱ ወራት የሚተከሉት 12 ዓይነት የፍራፍሬ ችግኞች ሲሆኑ እስካሁንም 450 ሚሊዮን የፍራፍሬ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
ችግኞቹም በዋናነት አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ አፕልና ብርቱካንን የሚያካትት ሲሆን ልማቱም በጅማ፣ በቡኖ በደሌ፣ በኢሉአባቦር፣ በ አራቱም የወለጋ ዞኖች፣ በጉጂ፣ በቦረና፣ በአርሲና በባሌ እንደሚከናወንም ለማሳያነት ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ጊዜ የመሬት መረጣና ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በአንዳንድ አካባቢዎች ተከላ መጀመሩንም ተናግረዋል።
በክልሉ የፍራፍሬ ልማት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉ ፍራፍሬዎች አሁን ላይ በሀገር ውስጥና በዓለም ገበያ ላይ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘት መጀመሩን ተናግረዋል።
በልማቱ ላይ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በቴክኖሎጂና በአቅርቦት አያያዝ ላይ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው የማይቋረጥ የባለሙያ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸውም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026