
ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሀላፊ በሪሶ ፈይሳ፤ በምርት ዘመኑ ሰፊ መሬትና የሰው ሃይልን በማቀናጀት በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብርና ልማት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በተያዘው መኸር 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 368 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት የሚያስችል የተቀናጀ የልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን ነው አቶ በሪሶ የገለጹት።
በመኸር እርሻ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑን ጠቅሰው ለምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር ስርጭት እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት አሁን ላይ በትራክተር እየለማ መሆኑንም ተናግረዋል።
በአንዳንድ አካባቢዎች ለደረሱ ሰብሎች የጥበቃና እንክብካቤ ከማድረግ በተጨማሪ የምርት አሰባሰብ ሂደቱ ብክነትን የሚቀንስ እንዲሆን እገዛና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል የገበያ ጥናት በማካሄድ ከባለሀብቱ ጋር የማገናኘት ስራ እየተከናወነ ይገኛልም ብለዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026