
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ በንግግርና በህግ አግባብ መልስ እንዲያገኝ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቷ ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ወደብ እንደሌላት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን አለባት የሚለው ጉዳይ ዘመን አመጣሽ አጀንዳ አለመሆኑን መገንዘብ እንደሚገባም አመልክተዋል።
ማንንም ሳንጎዳ የኛን ጉዳት መቀነስ እንዳለብን አምናለሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ በመሆኗ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት ተናግረዋል።
በዓለም በወደብ አልባ ሀገራት ልምምድ የሌለ ግፍ በኢትዮጵያ ላይ መፈጸሙንና ይህ ጉዳይ አፋጣኝ መፍትሄ ሊያገኝ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መግለጻቸው አይዘነጋም።
በማብራሪያቸውም፥ የባህር በር ጥያቄን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ኢትዮጵያ በባህር በር ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም እንዳላት ተናግረዋል።
ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ መንገድ ነው ብለውም ነበር።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ #Ethiopia
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026