
ነቀምቴ ፤ ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፤-በመኽር ወቅቱ በቆሎን በኩታ ገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆናቸውን በምስራቅ ወለጋ ዞን የጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
በምሰራቅ ወለጋ ዞን በዘንድሮ መኽር ወቅት 80ሺህ 820 ሄክታር ኩታገጠም ማሳ ላይ በቆሎ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታውቋል ።

በዞኑ በመኽር ወቅቱ ቀድመው ከሚዘሩ ሰብሎች አንዱ በቆሎ ሲሆን በዞኑ የጉቶ ጊዳ ወረዳ የኩታ ገጠም በቆሎ ልማት የዘር ስራ ዛሬ ተጀምሯል።
የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር አስፍው ለማ እንደተናገሩት የአካባቢው አርሶ አደሮች 1ሺ 33 ሄክታር መሬት ላይ በቆሎን በኩታገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ ዘር መዝራት ጀምረዋል ።
በቆሎን በተሻለ ጥራትና ብዛት በስፋት ለማልማት አቅደው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመው በግብርና ፅህፈት ቤት በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ወርቅነህ ገለታ በበኩላቸው ሰብልን በተናጠል ማልማት ውጤቱ እንብዛም መሆኑን ጠቁመው በኩታገጠም ማልማት አቅምን በማጎልበት የተሻለ ምርት እንደሚያስገኝ ተናግረዋል ።

አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም በመደራጀት አንድ ሺ ሄክታር መሬት ላይ በቆሎ በማልማት ከ80ሺ ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት አቅደው የዘር ስራ መጀመራቸውን አመልክተዋል ።
የምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አስፍው ሀንቢሳ በዞኑ በዘንድሮ መኽር ወቅት ከ80ሺ 820 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በበቆሎ ዘር የመሸፈን ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።
ለልማቱ የሚያገለግል 22ሺ ኩንታል የበቆሎ ምርጥ ዘር ቀርቦ እስካሁን ከ19ሺ ኩንታል በላዩ መከፍፈሉን ተናግረዋል ።

የማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭትም እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የሰብሉን ምርታማነት ለማሳደግ የእርሻ ስራውን የማዘመንና ለኩታገጠም አስተራረስ ዘዴ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል ።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026