የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት ይጥላል-የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት የሚጥል መሆኑን የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት ፓቲ መርቲን ገለጹ።


ፕሬዝዳንቷ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ እያደረገችው ያለውን የሪፎርም ስራ አድንቀዋል።


በተለይም በሀገር አቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የፋይናንስ ዘርፉን ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የወሰደቻቸው የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጥ በመፍጠር ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።


ሀገሪቷ ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለመገንባት እያደረገችው ያለው ጥረት ለኢንሹራንስ ዘርፉ ዕድገትና ቀጣይነት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።


በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ በሚፈለገው ደረጃ ዕድገት ባያስመዘግብም ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ ሀገራት በዘርፉ በትኩረት እየሰሩበት መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።


የኢንሹራንስ ገበያውን ተደራሽነት ለማስፋትም የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ነው ያብራሩት።


የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ዓለምን እየፈተኑ መሆኑን አንስተው፥ ለዚህ ደግሞ በቂ ምላሽ የሚሰጥና አደጋን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የኢንሹራንስ ተቋማትን መገንባት ይገባል ብለዋል።


ኢትዮጵያ ከአስተናገደችው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በተጓዳኝ ከተለያዩ የኢንሹራንስ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር በዘርፉ ስለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቷ አንስተዋል።


በቀጣይም በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ ለአጠቃላይ ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ሚናውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026