
አዲስ አበባ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለው ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለኢንሹራንስ ዘርፉ አስተማማኝ መሰረት የሚጥል መሆኑን የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ፕሬዚዳንት ፓቲ መርቲን ገለጹ።
ፕሬዝዳንቷ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ላይ እያደረገችው ያለውን የሪፎርም ስራ አድንቀዋል።
በተለይም በሀገር አቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የፋይናንስ ዘርፉን ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግ የወሰደቻቸው የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች ለውጥ በመፍጠር ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።
ሀገሪቷ ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ለመገንባት እያደረገችው ያለው ጥረት ለኢንሹራንስ ዘርፉ ዕድገትና ቀጣይነት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።
በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ በሚፈለገው ደረጃ ዕድገት ባያስመዘግብም ኢትዮጵያን ጨምሮ አንዳንድ ሀገራት በዘርፉ በትኩረት እየሰሩበት መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
የኢንሹራንስ ገበያውን ተደራሽነት ለማስፋትም የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ነው ያብራሩት።
የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ዓለምን እየፈተኑ መሆኑን አንስተው፥ ለዚህ ደግሞ በቂ ምላሽ የሚሰጥና አደጋን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የኢንሹራንስ ተቋማትን መገንባት ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከአስተናገደችው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ጉባኤ በተጓዳኝ ከተለያዩ የኢንሹራንስ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ጋር በዘርፉ ስለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቷ አንስተዋል።
በቀጣይም በአፍሪካ የኢንሹራንስ ዘርፉ ለአጠቃላይ ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ሚናውን እንዲያሳድግ እንሰራለን ነው ያሉት።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026