የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ከእንስሳት ሀብት ልማት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

May 28, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ግንቦት19/2017 (ኢዜአ)፦ከእንስሳት ሀብት ልማት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።


ሚኒስቴሩ ከአለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ''የኢትዮጵያ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ኢንቨስትመንት ሰነድ''ለክልልና በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት ለማስተዋወቅ ያዘጋጀው መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ የግብርና ኢንቨስትመንትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ በአገራችን ካለው ሰፊ የእንስሳት ሃብት አኳያ በዘርፉ በሚፈለገው መጠን ጥቅም እየተገኘ አይደለም።


ሀገሪቷ ካላት አቅም አንፃር ወደ ውጪ ከሚላከው የእንስሳት ተዋፅኦ እየተገኘ ያለው 130 ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚጠይቅ አመልክተዋል።


በኢትዮጵያ የአለም አቀፉን መስፈርትና ደረጃን ያሟሉ 10 ቄራዎች ቢኖሩም በእንስሳት አቅርቦት ችግር ሳቢያ የሚጠበቀውን ያህል እየሰሩ አለመሆኑን ተናግረዋል።


በመሆኑም ሀገሪቷ ያላትን ሀብት ወደ ቄራዎቹ በማምጣት የተሻለ ጥቅምና የውጭ ምንዛሪ ግኝታችንን ይበልጥ ማስፋፋት ያስፈልጋል ብለዋል።


የሌማት ትሩፋት ከተጀመረ ወዲህ መነቃቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እየተገኘ ቢሆንም በእንስሳት ዘርፉ ከቦታ ልየታ አንስቶ የቴክኒክ ድጋፍ ውስንነቶች እንዳሉ አመላክተዋል።


የግሉ ባለሀብትም በዘርፉ ለመሰማራት ያሳየው ቁርጠኝነት አነስተኛ በመሆኑ ተሳትፎውን ሊያሳድግ እንደሚገባ ጠቁመው፥ ወጣቶችንም በዘርፉ በስፋት በማሳተፍ ለስራ እድልና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት መጠናከር በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።


በዚህ ረገድም ሚኒስቴሩ የእንስሳት ሃብት ልማቱን ለማስፋፋትና ለማዘመን የሚያስችል ሰነድ ማዘጋጀቱን ጠቅሰው፥ ሰነዱ ሀገሪቷ በእንስሳት ዘርፍ ያላትን አማራጮች ያመላከተ መሆኑን ገልፀዋል።


በመሆኑም ሁሉም ክልሎች ካላቸው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በመቃኘት ስራ ላይ ማዋል እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።


በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ ግርማ ሙሉጌታ በበኩላቸው፥ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለስራ እድል ፈጠራ፣ የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ፣ ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃነት ለማዋል በሚያስችል መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።


የተዘጋጀው ሰነድም የኢንቨስትመንቱን እንቅስቃሴ በማነቃቃትና ኢትዮጵያን ከልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል ብለዋል።


በቀጣይም የእንስሳትና ዓሳ ንዑስ ዘርፎችን ወደ ዘመናዊ፣ተወዳዳሪ እና ለኤክስፖርት ብዝሃነት ቀጣይነት አይነተኛ መሳሪያነት ለመጠቀም ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026