የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

May 26, 2025

IDOPRESS

ሮቤ ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ) ፡-በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ የግንባታ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለጸ።


በብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።


ኃላፊው መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የክልሉ መንግሥት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች የሚመልሱና ተጠቃሚነቱን ለሚያረጋግጡ የግንባታ ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


በተለይ የህዝቡን የመልማት ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አመልክተዋል።


በሮቤ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችና ኢኒሼቲቮች የጥረቱ ማሳያዎችና ለብልጽግና ጉዞ ስኬት የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን አመልክተዋል።


የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው፥አስተዳደሩ ከተማውን ለነዋሪው ምቹ የመኖሪያ ቦታና የቱሪዝምና ንግድ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው።


አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ የከተማዋን የንግድ ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድጉ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።


የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝትም በዘርፉ የሚታዩ መልካም አጋጣሚዎችና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።


በአመራሮቹ ከተጎበኙ የልማት ፕሮጄክቶች መካከል የ''ሎላ ሻያ'' የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣የንብ ማነብና ዶሮ እርባታ ማዕከል ግንባታን ጨምሮ ሌሎች በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ የሚገኙ ኢኒሼቲቮች ተጎብኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026