
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር የጋራ ልማትና ትስስርን ማጠናከሩን ተገለጸ።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሽብሩ ማሞ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዲፕሎማሲው መስክ በዓለም አቀፍ መድረክ እውቅና እና ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት አገሮች ቅድሚያ የሚሰጥ እንደመሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትና ቀጣናዊ ትስስርን የበለጠ ለማጠናከር በመሰረተ ልማት፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት ከስድስት ዓመት በፊት በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለጎረቤት አገሮች ችግኝ በመስጠት፣ በመትከልና ልምድ በማካፈል ትስስርን ለማጠናከር ከሰራችው ጠንካራ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራዎች ውስጥ ተጠቃሽ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከጎረቤት አገሮች ጋር አብሮ የመልማት፣ የመበልጸግ፣ የተፈጥሮ ሃብትን በዘላቂነት በመጠበቅ በፍትሃዊነት የመጠቀም አቋሟን ያጠናከረችበትና በተሞክሮነት የተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።
የአየር ንብረት ለውጥን በዘላቂነት ለመከላከልና የተፈጥሮ ሃብትን ለመጠበቅ በመርሃ ግብሩ ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች በዓለም አቀፍ መድረኮች ልምዷን ማካፈሏንም ነው አምባሳደር ሽብሩ የገለጹት።
በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ያስመዘገበችው አስደናቂ ውጤት በዓለም አቀፍ መድረክ እውቅናን እንዳገኘ አስታውሰዋል።
በተለያየ የዓለም አገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች መርሃ ግብሩን የበለጠ ለማስፋትና ለማስተዋወቅ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
የጎረቤት አገሮች ከኢትዮጵያ ልምድ በመውሰድ ችግኝ እንዲተክሉ መነሳሳትን የፈጠረ በጎ ተጽዕኖ መፍጠሩን ገልጸዋል።
በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈጻሚ ፋኖሴ መኮንን በበኩላቸው፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተጎዳ መሬት እንዲያገግም፣ የመሬት እርጥበታማነት እንዲጨምር፣ የውሃ አካላት በመጠን እንዲጨምር ማድረጉን ዘርዝረዋል።
እንደ መሪ ስራ አስፈጻሚው ገለጻ፥በመርሃ ግብሩ 40 በመቶ የደንና 60 በመቶ የፍራፍሬ፣የእንስሳት መኖ፣ የአፈር ለምነትና ጤንነትን የሚጠብቁ ችግኞችን በመትከል ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና እንክብካቤ ልምድ በማካፈል ከጎረቤት አገሮች ጋር በትብብር የመልማት ጽኑ ፍላጎቷን ያሳየችበት እንደሆነም ተናግረዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ ችግኞች የታችኞቹ ተፋሰስ አገራት በጎርፍ አደጋ እንዳይጠቁ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ለ2017 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሰባት ነጥብ አምስት ቢሊዮን በላይ ችግኝ ዝግጅት መደረጉን አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026