የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉ የተጀመሩ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ነው - ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 14/2017(ኢዜአ)፦በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉ የተጀመሩ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።

“በዲጂታል የታገዘ ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ” በሚል መሪ ሀሳብ የመንግስት ተቋማት ተወካዮችን፣ የልማት አጋሮችን፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችን እና ባለሙያዎችን የተሳተፉበት አውደ ጥናት ተካሂዷል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ በዲጅታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ተጨባጭ ለውጥ ከመጣባቸው ዘርፎች ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አንዱ ነው።

ዘርፉን በዲጂታል ለማዘመን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን በመጥቀስ፥ በመንግሥትና በግል አጋርነት የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሳልጡ ቴክኖሎጂዎች መተግበራቸውን ተናግረዋል።

የዲጂታል ትራንስፖርት ማዕቀፍ፣ ስማርት መሰረተ ልማት፣ ዲጂታል የነዳጅ የክፍያ ስርዓት፣ ዲጂታል የትኬት መቁረጫና የክፍያ ዘዴ፣ ስማርት የመኪና ማቆሚያዎችና ዲጂታል የትራፊክ አስተዳደር ስርዓት መዘርጋታቸውን አንስተዋል።

በስትራቴጂክ ሪፎርም የተደገፉ አገልግሎትን የማዘመንና የማሻሻል ስራዎች የዘርፉን አጠቃላይ እንቅስቃሴና እድገት እየቀየሩት ነው ብለዋል።

የዲጂታል ክህሎት፣ መሰረተ ልማት፣ የሳይበር ደህንነትና ሌሎች ተግባራትን አጠናክሮ ለመጠቀልም የመንግሥትና የግሉ አጋርነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።

ዲጂታል ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ወደ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለሚደረገው ሽግግር ወሳኝ በመሆናቸው የቅንጅት ስራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።


የአይሲቲና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ይልቃል አባተ፥ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የተሰማሩ የግል ተቋማትና ባለድርሻ አካላት አገልግሎታቸውን ለማሻሻል የዲጅታል አሰራርን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል።

የራይድ መስራችና ስራ አስፈጻሚ ሳምራዊት ፍቅሩ በበኩላቸው፥ በትራንስፖርት ዘርፉ ዲጂታላይዜሽንን የሚደግፉ ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ገልፀዋል።


የዘርፉን አገልግሎት ይበልጥ ለማዘመንና የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት የመንግስትና የግል አጋርነት ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026