የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለምታደርገው ንቁ ተሳትፎ ፋይዳ ወሳኝ ሚና አለው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለምታደርገው ንቁ ተሳትፎ ፋይዳ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ዲጂታል ማንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው አይዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ዲጂታል ማንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ኢትዮጵያ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያድርግ ዘመናዊ፣ አካታች እና መሠረታዊ የዲጂታል ማንነት መለያ ስርዓት መዘረጋቷን ጠቁመዋል።

ፋይዳ ካርድ ብቻ ሳይሆን ልዩ የሆኑ ቁጥሮችን የያዘና ማንነት የሚረጋገጥበት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስካሁን ለ15 ሚሊዮን ዜጎች ተደራሽ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ፋይዳ ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው፤ ለሁሉም ዘርፎች ምቹ መደላደል ማድረጉንም ጠቁመዋል፡፡

ፋይዳን ለፋይናንስ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ቴሌኮም፣ የህዝብ አገልግሎቶች ከማህበራዊ ዋስትና ጋር በማስተሳሰር ተዓማኒ የሆነ መደላድል ለህዝቡ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ፋይዳ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈጣን የሆነ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ጠቁመው፤ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና እውን ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል፡፡

የዲጂታል ማንነት መለያ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዓላማው በህብረት በመሰለፍ የአፍሪካን እምቅ አቅም ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከኮንፈረንስ ማዕከልነት ባሻገር የራሷ ማንነት ያላት ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እጅግ ውብ በሆኑ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች እንዲሁም ከመልክዓ ምድሯ ልምድ መውሰድ የሚቻል ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡

ተሳታፊዎች ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱም ሁሉም ሰው አስተማማኝ የዲጂታል ማንነት መለያ እንዲኖረው በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡

በመድረኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘው ተሻገር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮችና የአለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026