
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ) ፡-የፋይዳ ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለን ነው ሲሉ በሠመራና አካባቢው የሚገኙ የመታወቂያው ተመዝጋቢዎች ተናገሩ።
በሠመራ ከተማ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መዝገባ በንቅናቄ መልክ በመከናወን ላይ ይገኛል።
በምዝገባ ሂደት ላይ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተመዝጋቢዎች መካከል የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ሳኒ አህመድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚሰሩ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል ጥቅሙ የጎላ ነው ብለዋል ።

ሌላዋ የሠመራ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሶፊያ አደም በበኩላቸው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን ጥቅሙ ብዙ መሆኑን በመረዳታቸው ለመመዝገብ መምጣታቸውን አብራርተዋል።

የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታችው እንደፈለጉ ተንቀሳቅሰው ለመስራትና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚረዳቸው የገለጹት ደግሞ የዱብቲ ከተማ ነዋሪ አቶ ማህሙድ ዓሊ ናቸው።

"ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለማግኘት የሚያችለን ነው" ያሉት ደግሞ የሠመራ ከተማ ነዋሪ አቶ ሁሴን መሐመድ ናቸው።

በኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ምስራቅ ሰመራ ሪጅን የሽያጭ ክፍል ኀላፊ አቶ ሃጎስ ወልደጊዮርስ በበኩላቸው ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የኢትዮጵያን የዲጂታል አለምን ጉዞ የሚያሳልጥ ቁልፍ መሣሪያ ነው ብለዋል።

እንደ አገር እየተከናወነ ያለውን የዲታላይዜሽን ጉዞ ለማፋጠንና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም አገልግሎቱ በተለያዩ ደረጃ የሚከናወኑ ማጭበርበሮችን የሚከላከል በመሆኑ በክልሉ የተለያዩ ማዕከሎች እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026