
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በቤተሰብ ደረጃ ኢኮኖሚን በማሳደግ ወደ ተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስገነዘበ።
የቤተሰብ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ በኢትየጵያ ደግሞ ለሶስተኛ ጊዜ "የተሻሻለ የቤተሰብ ሥራና ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሯል።
የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የቤተሰብ ኢኮኖሚ አቅምን ማሻሻል እና ጥሪት ግንባታን መደገፍ ይገባል።
በተለይም የፌዴራልና የክልል አስፈጻሚ አካላት የቤተሰብ የክህሎት ክፍተትን በመሙላት፣ የመስሪያ ቦታ እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለማቃለል በቁርጠኝነት እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
በሀገሪቱ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ የቤተሰብ ደህንነት ጥበቃ እና ጥሪት ግንባታ በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
ማንኛውም ቤተሰብ በሀገራዊ ብልጽግና እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ውስጥ አዎንታዊ ሚና እንዲኖረው ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።
ቤተሰብን ከድህነትና ከተረጂነት በማላቀቅ ወደ ምርታማነት እና የተሻለ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አንስተዋል።
ቤተሰብ በተነቃቃ የስራ ባህል ጥሪት በማፍራት፣ ኢኮኖሚውን በመገንባትና ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር በማሸጋገር ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026