የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ ይደረጋል

May 15, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ እንደሚሰራ የሲዳማ ክልል ኢንዱስረትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

ኮርፖሬሽኑ ከይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስረትሪ ፓርክ ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡

የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊና የኮርፖሬሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲያቀርቡ በማስቻል የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

ለፓርኩ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በግብዓትነት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮች ትስስር በማጠናከር ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።


በእስካሁኑ ሂደት ከፓርኩ ጋር ትስስር የተፈጠረላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው ምርቶቻቸውን በበለጠ ጥራትና ብዛት በማቅረብ የተሻለ ገቢ ማግኘት እንዲችሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በቀጣይ ሶስት ወራት ከፓርኩ ጋር ትስስር የተፈጠረላቸው 40ሺህ አርሶ አደሮች የምርቶቻቸውን ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችላቸውን ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

ሥልጠናው በምርት ሂደት፣ በአሰባሰብና አያያዝ ላይ የዘመነ አሰራር እንዲከተሉ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኃይሉ ዬቴራ፤ ፓርኩ ሥራ ከጀመረ አንስቶ በግብዓት ትስስርና በሥራ ዕድል ፈጠራ አርሶ አደሮችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ከሶስት ዓመት በፊት በፓርኩ የግብዓት ሰንሰለት ውስጥ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ትስስር የተፈጠረላቸው አርሶ አደሮች 36ሺህ እንደነበሩ ጠቅሰው በአሁን ወቅት ቁጥራቸውን 136ሺህ መድረሱን ተናግረዋል፡፡

በአሁን ወቅት በፓርኩ አቮካዶ፣ ወተት፣ ማርና ቡና የሚያቀነባብሩ ስምንት ኩባንያዎች በሥራ ላይ መሆናቸውን አንስተው ግብዓት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሥልጠናው እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል፡፡

በምክክር መድረኩ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የኮርፖሬሽኑ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኩና የኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026