
አዲስ አበባ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደርን አስመልክቶ ያዘጋጀው ኮንፈረንስ ዛሬ በቶጎ ሎሜ መካሄድ ጀምሯል።
ኮንፈረንሱ እየተካሄደ የሚገኘው “የአፍሪካ የመንግስት የእዳ አስተዳደር አጀንዳ፤ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን የሚያረጋግጡ ስትራቴጂዎችን መተግበር” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
በመክፈቻው ስነ ስርዓት ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ሞሰስ ቪላካቲ፣ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማህማ የአፍሪካ ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የአፍሪካ ፋይናንስ ተቋማት፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በአፍሪካ ወቅታዊ የእዳ ሁኔታ ላይ በመምከርም የሀገራት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ተሞክሮ መለዋወጥ እና አፍሪካ በእዳ የጋራ አቋም ለመያዝ የሚያስችላት ምክረ ሀሳቦች ማቅረብ የኮንፈረንሱ ዋንኛ አላማ መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው ያመለክታል።
በአህጉሪቷ ላለው የእዳ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት አሁናዊ የዓለም የፋይናንስ መዋቅር መደረግ የሚገባቸውን ሪፎርሞች በተመለከተም ውይይት ይካሄዳል።
ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ይደረጋል።
በአፍሪካ ዘላቂ የእዳ አስተዳደርን ለመፍጠር የሚያስችሉ ውጤታማ የእዳ አስተዳደር አማራጮችን በተመለከተ የመፍትሄ አማራጮች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
ውይይቱን ተከትሎ የአፍሪካ ሀገራት የእዳ አስተዳደር፣የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻያ እና ዘላቂ የፋይናንስ አስተዳደርን አስመልክቶ የጋራ አቋም መግለጫ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
የአፍሪካ ህብረት የዘላቂ እዳ አስተዳደር ኮንፍረንስ እስከ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026