
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦የወላይታ ሶዶ ግብርና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የውስጥ ገቢውን እያሳደገ መሆኑን አስታወቀ።
የኮሌጁ ዲን አሉላ ታፈሰ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ሥራ በተጨማሪ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በእንስሳትና በዶሮ ልማት ውጤታማ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የሚያመርታቸውን ምርቶች ለማህበረሰቡ ከማቅረብ ባለፈ በዘርፉ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሳደግ ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የሥጋ ዶሮዎችን፣ እንቁላልና የወተት ምርቶችን ጨምሮ የተለያዩ አትክልቶችን በማምረት ለአካባቢው ነዋሪዎች በቅናሽ ዋጋ በማቅረብ ገበያ የማረጋጋት ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል።
ኮሌጁ የወተት ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ገልጸው፣ በዚህም ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት ከማጠናከር ባለፈ የኮሌጁን የውስጥ ገቢ እያሳደገ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ በሚያከናውናቸው የሌማት ትሩፋት ሥራዎች ከ100 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አሉላ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ሰፋፊ ሥራዎች መጀመራቸውን የገለጹት ደግሞ በኮሌጁ የእንስሳት እርባታ ባለሙያ አቶ በረከት በቀለ፥ ህብረተሰቡ በኮሌጁ የሌማት ትሩፋት ሥራ በተለያየ መንገድ ተጠቃሚ እየሆነ ነው።
ኮሌጁ ምርቶችን በዝቅተኛ ዋጋ ከማቅረብ ባለፈ በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ለሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ስኬታማነት የበኩሉን እየተወጣ መሆኑንም አመልክተዋል።
ኮሌጁ ወተትና እንቁላልን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን እያረጋጋ መሆኑን የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ማለዳወርቅ ሉቃስ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ናቸው።
ህብረተሰቡ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዘላቂነት ተጠቃሚ እንዲሆን ግንዛቤውን ከማሳደግ ባለፈ የዘር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ሻሼ ሻጎ የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፥ ኮሌጁ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እያከናወነ ባለው ተግባር የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በጥቃቅን የችርቻሮ ንግድ ሥራ ተሰማርቼ በማገኛት ጥቂት ገንዘብ ቤተሰብ ለማስተዳደር እቸገር ነበር ያሉት ወይዘሮ ሻሼ፣ አሁን ላይ በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል በሚያገኙት ገቢ ያለስጋት ኑሯቸውን እየመሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የወላይታ ሶዶ ግብርና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ የተሻሻሉ የግብርና አሰራርና ቴክኖሎጂዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ሥራውን ለማስፋፋት ግብ ጥሎ እየሰራ መሆኑም ታውቋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026