የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ሚኒስቴሩ

May 12, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 1/2017(ኢዜአ)፦ የአከባቢ ብክለትን ለመከላከልና ተፅዕኖውን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

5ኛው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ሲምፖዝየም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር)፤ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመሆኑም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት እገዛቸው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።


የምርምር ሲምፖዚየሙ ዓላማም የፕላስቲክና የወረቀት ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እንዲሁም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን አያያዝ፤ መልሰው መጠቀምና ወደ ሃብት መቀየርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።


የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ተሾመ አብዶ(ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከማፍራት ባለፈ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በተለይ በህዋ ሳይንስ፤ ፋርማሲዩቲካል፤ ድሮን ቴክኖሎጂና አውቶሞቲቭን ጨምሮ አምስት የልህቀት ማዕከላትን ወደ ሙሉ የምርምር ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው 20 ክልላዊና የፌዴራል ሜጋ ፕሮጄክቶችን የማማከር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአይሲቲ መሰረተ ልማት ዝርጋታና በሶፍትዌሮች ልማት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በምርምር ሲምፖዝየሙ ከሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች፤ ከደቡብ ኮሪያ፤ ከህንድና ከአውስትራሊያ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026