
አዳማ፤ ግንቦት 1/2017(ኢዜአ)፦ የአከባቢ ብክለትን ለመከላከልና ተፅዕኖውን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።
5ኛው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ሲምፖዝየም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር)፤ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ስራዎች የማህበረሰቡን ችግሮች የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በመሆኑም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ለሚደረገው ጥረት እገዛቸው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።

የምርምር ሲምፖዚየሙ ዓላማም የፕላስቲክና የወረቀት ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እንዲሁም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን አያያዝ፤ መልሰው መጠቀምና ወደ ሃብት መቀየርን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ተሾመ አብዶ(ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ከማፍራት ባለፈ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በተለይ በህዋ ሳይንስ፤ ፋርማሲዩቲካል፤ ድሮን ቴክኖሎጂና አውቶሞቲቭን ጨምሮ አምስት የልህቀት ማዕከላትን ወደ ሙሉ የምርምር ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው 20 ክልላዊና የፌዴራል ሜጋ ፕሮጄክቶችን የማማከር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአይሲቲ መሰረተ ልማት ዝርጋታና በሶፍትዌሮች ልማት ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በምርምር ሲምፖዝየሙ ከሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች፤ ከደቡብ ኮሪያ፤ ከህንድና ከአውስትራሊያ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ተሳታፊ ሆነዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026