የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተሞች የትብብር መድረክ ልምዶችን በመለዋወጥ የተሻለ ግብዓት የሚገኝበት ነው

May 7, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ከተሞች ልምዳቸውን በመለዋወጥ ለእድገታቸው የተሻለ ግብዓት እያገኙበት መሆኑን ገለጹ።

በኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ አዘጋጅነት የአራት ክልሎች ከተሞች ከንቲባዎች የተሳተፉበት ስልጠናዊ አውደ ጥናት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይም የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ዋና ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ጤናው እንደገለጹት የከተሞችን የእርስ በርስ ትስስር በማጠናከር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ ነው።

በተለይም ከተሞች የውስጥ ገቢያቸውን በማሳደግ የህዘቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሊመልሱ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የትብብር መድረኩ 108 አባል ከተሞችን በአባልነት መያዙን ጠቅሰው በመድረኩም ከተሞች ልምድ እየተለዋወጡ ለእድገታቸው የተሻለ ግብዓት እያገኙበት መሆኑን አስረድተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ የምስራች ገመዴ በበኩላቸው የትብብር መድረኩ እያደገ የመጣውን የነዋሪዎች የአገልግሎትና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተሻለ ልምድ የሚቀሰምበት መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ከተሞችን በማዘመን ለነዋሪዎች ምቹና ጽዱ ለማድረግ እንዲሁም የቱሪስት መዳረሻነታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ(ዶ/ር) በከተማው የኮሪደር ልማትና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በተጨማሪም የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግ የሚያግዙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም እየተተገበሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

ለሁለት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ የ22 ከተማ ከንቲባዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026