አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስና ቀረጥ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባው የገቢዎች ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ገምግሟል።
በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በገቢዎች ሚኒስቴር ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ገቢ እንዲጨምር ማድረጉን አመልክቷል።
የታክስና ቀረጥ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ነው የጠቆመው።
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በገቢ አሰባሰብ፣ በታክስ ህግ ተገዥነት፣ በኮንትሮባንድ ቁጥጥርና ሌሎች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አቅርበዋል።
ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 646 ነጥብ 72 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 653 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል።
አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ279 ቢሊዮን ብር ወይንም ከ74 በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
ከተሰበሰበው ገቢ የሀገር ውስጥ ታክስ 345 ነጥብ 93 ቢሊዮን ብር፣ የውጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ 307 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ድርሻ እንደሚይዙ ጠቁመዋል።
እንደሚኒስትሯ ገለጻ፤ ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ በተሻሻለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀመር መሰረት 61 ነጥብ 13 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የተላለፈ ሲሆን፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ እድገት አሳይቷል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 15 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ-ወጥ ገንዘብ መያዙንም ተናግረዋል።
ገቢን መደበቅ፣ ግብይትን ያለደረሰኝ ማከናወን፣ ኮንትሮባንድ፣ የግብር ስወራና የታክስ ማጭበርበር አሁንም የታክስ አስተዳደር ችግሮች መሆናቸውን አንስተዋል።
ህገ ወጥነትን ለመከላከል በግብይት ወቅት ደረሰኝ በማይቆርጡ 616 ድርጅቶች ላይ ኦፕሬሽን በማከናወን 597 ተጠርጣሪዎች ለህግ በማቅረብ በወንጀል ምርመራና ክስ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
የምክር ቤት አባላት በቀረበው ሪፖርት ላይ በታክስና ጉምሩክ ህግ ተገዥነት፣ የታክስ ምንጭ ከማስፋት፣ ኮንትሮባንድን ከመከላከልና ህገ-ወጥ ኬላን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ አስተያየትና ጥያቄዎችን አንስተዋል።
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና የታክስ ምንጮችን ለማስፋት ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ተግባራት መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው፤ ህገ-ወጥ ኬላዎችን በጥናት መለየታቸውን ገልጸው፤ ችግሩን ለመከላከል ከጸጥታ አካላት፣ ከፍትህ ተቋማትና ከክልሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጆ በሚኒስቴሩ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ገቢ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው አኳያ የሚሰበሰበውን ገቢ የበለጠ ለማሳደግ የታክስና ቀረጥ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
በተመሳሳይ የታክስ መሰረትን ማስፋት፣ ከክልሎች ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፣ ከቀረጥ ነጻ የሚገቡ እቃዎች ለታለመላቸው አላማ መዋላቸውን ማረጋገጥ ትኩረት እንዲሰጣው አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025