
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ኢትዮጵያ ባንኩን ለመቀላቀል ያቀረበችውን ጥያቄ መቀበሉን አስታወቀ።
ባንኩ ኢትዮጵያ አባል ለመሆን የሚያስችላትን የድርድር ሂደት እንድትጀምር ጋብዟል።
ይህ ለኢትዮጵያ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ትልቅ ስኬት የሚባል መሆኑን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ከባንኩ ፕሬዝዳንት ዲልማ ሩሴፍ ጋር መወያየታቸው የሚታወስ ነው።
በውይይቱም ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን የፋይናንስ ትብብር እና ከባንኩ ጋር በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ እንደሆነች መግለጿን ኤምባሲው በመረጃው አስታውሷል።
ኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (በቀድሞ አጠራሩ የብሪክስ ልማት ባንክ) በብሪክስ አባል ሀገራት እ.አ.አ በ2014 ተቋቁሞ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2015 ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026