የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢንዱስትሪዎች በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ በመታገዝ መስራት አለባቸው

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፦ኢንዱስትሪዎች በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዘው ጥራቱን የጠበቀ ምርት ማምረት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሦስተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።


በዚህም የኤክስፖው አካል የሆኑ ፓናል ውይይቶች በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በመድረኩ በአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ላይ ያተኮረ ውይይ ተካሂዷል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ኢንዱስትሪዎች በምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ሊታገዙ ይገባል፡፡


ከለውጡ በኋላ የተጀመረው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂና የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ፕሮግራም የዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት ከማዳበር ባለፈ ለግሉ ዘርፍ ምቹ አውድ የፈጠረ ነው ብለዋል።


ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበት የ4ጂ እና 5ጂ ኔትወርክ ተደራሽ በማድረግና የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ በማድረግ ረገድም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡


በዚህም ግልጽነትና አስተማማኝነት ያለው አገልግሎት የሚሰጡ ኦንላይን ፕላትፎርሞች መፈጠራቸው በዘርፉ ለተገኙ ለውጦች ማሳያ መሆናቸውን አመላክተዋል።


የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ለመቀነስ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡


የፈጠራ ውጤቶች ለማስፋትና የፈጠራ ሃሳቦችን በማዳበር ወደ ተግባር ለመቀየር በኢኖቬሽን ማዕከላት እና በዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ሊንኬጅ አማካኝነት የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል።


ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች በፈጠራ ውጤታቸውና በቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸው ለአነስተኛና መለስተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርጥ ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ በጥናትና ምርምር የመደገፍ ስራ በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026