
ጅማ፣ሚያዚያ 27/2017(ኢዜአ)፦የንብ ማነብ ስራን በዘመናዊ መንገድ በማከናወን የማር ምርትን ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
በጅማ ከተማ የማር ኤግዚቢሽን የተከፈተ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ ላይ የፌዴራል፣የክልልና የዞን የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም ማር አምራቾችና ነጋዴዎች ተሳትፈዋል።
ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ ያላት ሀገር ናት።
ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ባህላዊውን የንብ ማነብ ስራ ወደ ዘመናዊ መቀየሩ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በኦሮሚያ ክልል ለማር አምራቾች ዘመናዊ ቀፎ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የማር ምርትን ለማዘመን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱን የገለጹት ሚኒስትሩ ከዚህም 250 ሺህ ቶን የማር ምርት ተገኝቷል ብለዋል።
የንብ ማነብ ስራን የበለጠ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናከሩ አስታውቀዋል።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ጉቱ ገመቹ በበኩላቸው፥ በክልሉ ከአራት አመት በፊት የተጀመረው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ትልቅ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
እየተካሄደ በሚገኘው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ባህላዊ የንብ ቀፎን በዘመናዊ በመተካት የማር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
በክልሉ የማር ምርትን ለማሳደግ በተደረገ እንቅስቃሴ በዚህ አመት 140 ሺህ ቶን ማር መገኘቱን ተናግረዋል።
የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ በዞኑ በግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል::
በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች እየተተገበሩ ያሉ ኢኒቬቲቮች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፥ በማር ምርትም የተሻለ እመርታ መታየቱን ጠቅሰዋል።
በማር ምርት ኢግዚቢሽኑ የተሳተፉ አምራቾች በበኩላቸው፥ መንግስት በተመጣጣኝ ዋጋ ባቀረበላቸው የዘመናዊ ቀፎ ምርታቸው መጨመሩን ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026