
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ከተማዋን ውብ ገፅታ ያላበሱና የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ የቀየሩ ናቸው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች አዲስ አበባን ዘላቂነት ባለው አግባብ ለዜጎች ምቹ እና ውብ እያደረጓት ይገኛል።

ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከመሰረቱ ከመቀየር ባሻገር ለነዋሪዎቿ ምቹና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆን እያንደረደራትም ይገኛል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን አስመልክቶ ከነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡
አቶ ኤርሚያሰ ተገኔ በመዲናዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋን ውብ ገፅታ ያላበሱና የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ የቀየሩ ናቸው ፣ ለሰው ልጆች ምቹ እና አስፈላጊ በሆነ መልኩ መገንባቱን ተናግረዋል።
የተገነቡት የመናፈሻ ቦታዎች፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች የራስን ጤና ከመጠበቅ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳላቸው ነው የተናገሩት ።

የፈረንሳይ ለጋሲዮን ነዋሪ የሆነችው ሃይማኖት አብርሃም በበኩሏ በከተማዋ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች አበረታች ናቸው ብላለች።
በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች የተሰሩ የልማት ስራዎች እንዳይበላሹ ነዋሪዎች በሃላፊነት መጠቀም እና መንከባከብ እንዳለበት ተናግራለች።
አቶ ሀይለማርያም ኪዳኔ ለ40 አመታት በካዛንችስ አካባቢ መኖራቸውን ተናግረው ከዚህ ቀደም የነበረውን የአካባቢውን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የቀየረና ውብ ገጽታ ያላበሰ ግንባታ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

በካዛንቺስ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች እጅግ የሚደነቁና አስደናቂ ውበት የተላበሱ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

እየተሰራ ያሉ ስራዎች ትውልድን ማዕከል ያደረጉ በመሆናቸው የሚበረታታ ነው ያሉት የመዲናዋ ነዋሪ የሆኑት አቶ ዘላለም ጀምበሩ ናቸው።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026