የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ5ሺህ 430 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ5ሺህ 430 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ ገልጸዋል፡፡


ከማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4ሺህ 725 ነጥብ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት ታቅዶ 5ሺህ 436 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

ይህም ከዕቅዱ የ710 ነጥብ 94 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ15 ነጥብ 04 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 61 በመቶ ብልጫ እንዳለውም አስታውቀዋል፡፡


አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት የሚያስችሉ የፍተሻና የክትትል ሥራዎች በየጊዜው መከናወናቸው፣ የኦፕሬሽን ሥራው የተቋሙ ሥራ አመራር ባፀደቀው የኦፕሬሽን ሥራዎች የአሰራር ስርዓት ማኑዋል መሰረት መከናወኑ እና የኃይል መቋረጥ አመላካቾችና ችግሮች(alarms and faults) ሲስተዋሉ ወዲያውኑ እንዲወገዱ መደረጋቸው ለውጤቱ ምክንያቶች ናቸው ብለዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 6ሺህ 141 ነጥብ 49 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አስታውሰው ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከአጠቃላይ ዕቅዱ የ88 ነጥብ 52 በመቶ አፈጻፀም ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት፡፡

ይህም በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት አመላካች እንደሆነም አቶ ደጀኔ ጉታ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026