
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር በኢትዮጵያ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እንደተዘጋጀም ተገልጿል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።
የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እየተዘጋጀ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።
ይህም ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውንና በቅርቡ ወደ ስራ የሚገባውን የስታርታፕ አዋጅ ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚረዳ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
በተጨማሪም የስታርታፕኢንኩቤሽን ሞዴሎችን ማሻሻል እና የስታርታፖች አቅም ማጠንከርና የፈንድ ምንጮችን ለመጨመር መግባባት ላይ ተደርሷል።
ሚኒስትር ዴኤታው እና ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ ያሉ ስታርታፖች በአውሮፓና ፈረንሳይ የስታርታፕ ስነምህዳር እንቅስቃሴዎች ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉብት ዕድል በሚፈጠርበት ሁኔታ ላይ በጋራ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026