የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር የሚያስችል ውይይት ተደረገ

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር በኢትዮጵያ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ(ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እንደተዘጋጀም ተገልጿል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ ባዳዳ(ዶ/ር) ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሉዊስ አንቶኒ ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የጀማሪ ስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ሥነ-ምህዳር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ ከአውሮፓ ህብረት እና ኤክስፐርቲስ ፍራንስ ጋር በመተባበር የስታርታፕ ሥነ-ምህዳሩን ለማጠናከር10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ እየተዘጋጀ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።

ይህም ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውንና በቅርቡ ወደ ስራ የሚገባውን የስታርታፕ አዋጅ ወደ ተግባር ለማሸጋገር እንደሚረዳ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

በተጨማሪም የስታርታፕኢንኩቤሽን ሞዴሎችን ማሻሻል እና የስታርታፖች አቅም ማጠንከርና የፈንድ ምንጮችን ለመጨመር መግባባት ላይ ተደርሷል።

ሚኒስትር ዴኤታው እና ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ ያሉ ስታርታፖች በአውሮፓና ፈረንሳይ የስታርታፕ ስነምህዳር እንቅስቃሴዎች ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉብት ዕድል በሚፈጠርበት ሁኔታ ላይ በጋራ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026