የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ 4ኛው ክልላዊ የስራ ፈጠራ ውድድር መርሃ ግብርን አስጀመሩ

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ 4ኛው ክልላዊ የስራ ፈጠራ ውድድር መርሃ ግብርን አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ውድድሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በቴክኒክ ሙያ ኮሌጆች መምህራን እና ተማሪዎች የሚዘጋጁ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉ ሊሆኑ ይገባል።

በውድድሩ 12 የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች 34 መምህራን፣ 59 ተማሪዎች እና 2 የግል ድርጅቶች መቅረባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።


በተወዳዳሪዎቹ ተዘጋጅተው ከቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች መካከል የእርሻ ምርት መሰብሰቢያ ማሽኖች፣ የዶሮ መፈልፈያ፣ የእንስሳት መኖ ማዘጋጃና ለቤት ግንባታ የሚውሉ ግብዓቶች እንደሚገኙበትም ተጠቁሟል።

ለውድድሩ የሚቀርቡ የፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆን እንደሚገባቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

በውድድሩ ላይ ለእይታ የቀረቡ ምርቶች የክልሉን ህዝብ የእለት ተእለት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉና የወጣቶችን የስራ ፈጠራ ባህል የሚያበረታቱ እንዲሆኑም አስገንዝበዋል።

በፈጠራ ላይ የሚሰማሩ ሰዎች የሚሰሯቸውን ሥራዎች ለመደገፍ የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።


የሶማሌ ክልል የክህሎትና ሥራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ 4ኛ ዙር ዓመታዊ የቴክኒክ ኮሌጆች ያቀረቡት ምርቶች ለግብርና፣ ለእንስሳት እርባታና ለስራ ፈጠራ የላቀ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱና አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች የቀረበበት ነው ብለዋል።

ለሶስት ቀናት የሚቆየው ይህ ውድድር "ጤናና አምራች ዜጋ ለሁለንተናዊ እድገት መሰረት ነው" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚቆይ ሲሆን በውድድሩ ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች እውቅና እና ሽልማት እንደሚበረክት ገልጸዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ፣ የክልሉ የክህሎትና ስራ እድል ፈጠራ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌይድ፤ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አደንና ሌሎች አመራሮች መገኘታቸው ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026