የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአዲስ አበባ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና የስራ ባህልን የቀየሩ ናቸው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2017 (ኢዜአ)፡-በአዲስ አበባ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና የስራ ባህልን የቀየሩ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተጠሪ ተቋማት እና የብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገለጹ።

የልማት ሥራዎቹ የመዲናዋን ገፅታና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተጠሪ ተቋማት እና የብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በዚህም በኮሪደር ልማት፣በመልሶ ማልማት፣በወንዝ ዳርቻ፣ የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል፣ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉት የፌዴራል ስነምግባር እና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን የህዝብ ግንዛቤ ማጎልበቻ መሪ ስራ አስፈጻሚ ነጅመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እየተከናወኑ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል።

ከዚህም ባሻገር ቀን ከሌሊት ፕሮጀክቶችን በመፈጸም የሥራ ባህል ለውጥ መምጣቱን የጠቀሱት ዶክተር ነጅመዲን፥ የልማት ስራዎቹ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው ብለዋል።

የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዚዳንት አባንግ ኩመዳን፥ በሁሉም ዘርፎች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በመዲናዋ ምቹ የመኖሪያ፣ የመዝናኛና የሥራ ከባቢ እየፈጠሩ መሆኑን ተናግራለች።

ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ዕድገት የሚያፋጥኑ እንዲሁም የተቀናጁ መሠረተ ልማቶችን ያካተቱ መሆናቸውም የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የብቃትና የሰው ሃብት መሪ ስራ አስፈፃሚ ገዛኸኝ መጎ በበኩላቸው፥ የልማት ስራዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ መጠናቀቃቸው የፕሮጀክት የመፈጸም አቅም እያደገ ለመምጣቱ ሁነኛ ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡

በከተማዋ የኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች የአዲስ አበባን ገፅታ እየቀየሩ መሆኑን እንደተመለከቱም ጠቅሰዋል።

የልማት ሥራዎቹ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ እንደሚሳካ ተጨባጭ ማሳያ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር የአስተዳደር ዘርፍ አማካሪ ሙሉጌታ ሰይፈ ናቸው።

አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም፥ በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡

የልማት ስራዎቹ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን በማንሳት በፕሮጀክቶቹ ውስጥ በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል።

ህብረተሰቡም ለልማት ስራዎቹ ስኬታማነት እያደረገ የሚገኘውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026