
አንዳንዶቹ ከመደበኛ ግብርና ጎን ለጎን ያከናውኑታል ሌሎቹ ደግሞ ብቻውን የሙሉ ጊዜ ስራቸው መተዳደሪያቸው ያደርጉታል።
በደቡብ ምዕራብ ክልሏ ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በአንድ ቀበሌ ውስጥ ብቻ በ110 ዘመናዊ እና በ160 ባህላዊ የንብ ቀፎዎች እየተከናወነ ያለው የንብ ማነብ ስራ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን አርሶ አደሮቹ ይናገራሉ።
ኤላ ባቾ በተባለችው ቀበሌ ያሉት አርሶ አደሮቹ የማር ምርታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱም ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።

የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽሕፈት ቤትም በዘርፉ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ሁለንተዊ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን ገልጿል።
በጽሕፈት ቤቱ እንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ገበየሁ እንደሚያስረዱት ቀደም ሲል ከአንድ ባህላዊ ቀፎ ከ4 እስከ 5 ኪሎ ግራም ማር ይገኝ ነበር።
አሁን በስፋት እየተሰራበት ባለው የሽግግር ቀፎም ከ20 እስከ 25 ኪሎ ግራም ማር እየተገኘ መሆኑን ያስረዳሉ።
ለዚህ ደግሞ ከቀፎ አዘገጃጀት ጀምሮ እስከ ማር ቆረጣ ድረስ በዘርፉ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች ጋር በመሆን ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026