የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመዲናዋ ለበዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት በበቂ መጠን ቀርበዋል - ሸማቾች

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ ለትንሳኤ በዓል የሚሆኑ የእርድ እንስሳት በበቂ መጠን መቅረባቸውን ኢዜአ ሲገበያዩ ያገኛቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለፁ።

ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የእርድ እንስሳት የግብይት ሁኔታን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

በዚህም የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦት በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።

በሾላ ገበያ ዶሮ እና እንቁላል ሲገበያዩ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ እመቤት ታደሰ፤ ለበዓሉ በቂ የእንስሳት አቅርቦት እንዳለ አስተያየታቸው ሰጥተዋል።

በቂ አቅርቦት መኖሩ ሁሉም ባለው አቅም መርጦ በመግዛት በዓሉን እንዲያከብር ያስችለዋል ሲሉ ነው የጠቀሱት።

በአዲሱ ገበያ ሲገበያዩ ያገኘናቸው አቶ ይታገሱ በቀለ እና ስዩም ተፈራ በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የትንሳኤ በዓል መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ቢኖረውም ገበያው ላይ በቂ አቅርቦት በመኖሩ እንደአቅማቸው መግዛታቸውን ገልጸዋል።

የበግና ፍየል ገበያ ከሌሎቹ የበዓል ጊዜያት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ቢያሳይም ከአርሶ አደሮቹ በጥሩ ዋጋ መግዛት መቻላቸውን አቶ ዘሪሁን ወልዴ የተባሉ ሸማች ተናግረዋል።

አቶ ምሳዬ ተፈራ፣ አቶ አንዷለም እሸቴ እና አቶ ዘለቀ እጅጋየሁ በሰንጋ ገበያው በቂ አቅርቦት መኖሩን ነው የተናገሩት።

አስተያየት ሰጪዎቹ በአሉን ስናከብር ጧሪ የሌላቸውንና አቅመ ደካማ ወገኖችን በመጠየቅና ካለን በማካፈል ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የበዓሉ አስተምህሮም ይህንኑ የሚያጎለብት መሆኑን አመልክተው፤ የበዓሉን እሴት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026