የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ እና ቬይትናም አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ራዕይ ይዘው እየሰሩ ነው

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ቬይትናም አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ራዕይ ይዘው እየሰሩ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ገለጹ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቬይትናም ቆይታን አስመልክቶ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ቬይትናም ከ20 እና 30 ዓመት በፊት በጦርነት የተጎዳች ሀገር ብትሆንም አሁን ላይ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ መሰለፏን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ የልማት ትልሟን ለማሳካት የረጅም፣ የመካከለኛ እና የአጭር ጊዜ ዕቅድ አውጥታ እየሰራች መሆኑን ጠቅሰው፣ ቬይትናምም በተመሳሳይ የልማት ዕቅዷን ለማሳካት ባደረገችው ትጋት ውጤታማ ሆናለች ብለዋል።

ሀገሪቱ በኢንዱስትሪና ኮንስትራክሽን ዘርፎች ባሳየችው እመርታ የዓለም የምርት ማዕከል መሆን መቻሏንም ነው ያነሱት፡፡

ለዚህ ውጤት መመዝገብ ዕቅድን በአግባቡ ለመፈጸም መንግስት ያሳየው ቁርጠኝነትና የህዝብ ድጋፍ መሆኑን ነው ያነሱት።

ኢትዮጵያም በአጭር ጊዜ ውስጥ ብልጽግናዋን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለችው ጥረት ውጤታማ እንደሚሆን ከቬይትናም ልምድ የወሰደችበት ነው ብለዋል።

እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፤ ኢትዮጵያ እና ቬይትናም አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ተመሳሳይ ራዕይ ይዘው እየሰሩ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ኢትዮጵያ ንጹህ፣ አረንጓዴ፣ ለኑሮ አመቺና ዘላቂ ከተማ ለመገንባት እያደረገች ያለችው ጥረት ከቬይትናም ጋር እንደሚያመሳስላትም ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ስማርት ሲቲ ግንባታ ላይ ቬይትናም ያላትን ልምድ መቅሰም መቻሉንም ነው ዶክተር እዮብ ተካልኝ ያብራሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026