የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቬይትናም በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች ተደርገዋል - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በቬይትናም ቆይታ በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቬይትናም ቆይታን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ቬይትናም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀጣይነት ያለው እድገት በማስመዝገብ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሀገራት የገባች መሆኗን አንስተዋል።

በተለይም የግብርና ልማቷን በማዘመን ትልቅ እድገት ማስመዝገቧን ተናግረዋል።

ባለፉት 20 እና 30 አመታት በግብርና ላይ በሰራችው ስራ አሁን ላይ በአለማችን ከፍተኛ የቡና አምራች እና ላኪ ሀገር መሆን መቻሏንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያም አንዷ ከፍተኛ የቡና አምራች ሀገር መሆኗን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ቬይትናም በሩዝ እና በአትክልት እንዲሁም ፍራፍሬ ትልቅ አቅም መፍጠሯን አንስተዋል።

ቡና ኤክስፖርት በማድረግ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደምታገኝ ጠቅሰው፤ ከዚህም ብዙ ልምድ መውሰድ እንደሚቻል ተናግረዋል።

የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻርም በተለይ በሩዝ ላይ ትልቅ ስራ መስራቷን ለመመልከት መቻሉን ገልጸዋል።

በ7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ በማልማት 24 ሚሊዮን ቶን ምርት እንደምታገኝ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያም ባለፉት ሁለት አመታት ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ ማምረት መጀመሯን በመግለጽ።

በቬይትናም ቆይታም በስንዴ የተሰራውን ስራ በሩዝ ላይ መድገም የሚያስችል የተሞክሮ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አንስተዋል።

በሩዝ ምርት እና የእሴት ሰንሰለት ላይ በጋራ ሰፋፊ ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶች መደረጋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።

ከአትክልት እና ፍራፍሬ ስራዎች አንጻር የሚወሰደው ተሞክሮ ምርቶቹ ሳይበላሹ የሚጓጓዙበት ስርዓት መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ምርቶቹን ከመነሻቸው ጀምሮ የሚሰበሰቡበት መንገድም ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን እና ይህም የድህረ ምርት ብክነት የቀነሱበትን መንገድ እንደሚያሳይም ተናግረዋል።

በታዳሽ ሀይል፣ በስማርት ሲቲ ግንባታ እንዲሁም ከተፈጥሮ ጋር የተላመደ የአኗኗር ዘዴያቸው አስደናቂ መሆኑን በመጥቀስ።

ቀጣይነት ያላቸውን ስራዎች ማከናወን ከተቻለ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ አደገ ኢኮኖሚ መሻገር እንደሚቻል ቬይትናም ማሳያ መሆኗንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026