
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ)፦ ኮሪደር ልማትና ተያያዥ ግንባታዎች ከከተሞች የወደፊት ዕድገት ጋር የተሳሳሩ ናቸው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሃላፊው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ከክልላችን አመራሮች፣ ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ከደብረብርሃን ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራና ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ አድርገናል ብለዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ የኮሪደር ልማት መጀመሪያው ምዕራፍ ከጠባሴ መሳለሚያ እስከ በሬሳ ድልድይ ድረስ የ3 ኪሜ ግንባታ መሆኑን ገልጸው ይህም የመንገድ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድን እንዲሁም መናፈሻዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።
በተቀናጀ የአመራር ክትትል የመጀመሪያውን ምዕራፍ ቀሪ ስራዎችን በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ደብረ ብርሃን ከተማን ውብ ገጽታ በማላበስ ለኑሮ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹነቷን የሚያሳድግ እንደሚሆን ገልጸው በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደርና በክልሉ መንግስት ትብብር እየተከናወነ ያለውን ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ግንባታ ሂደት መመልከታቸውን ጠቁመዋል።
የገበያ ማዕከሉ በተጀመረበት የግንባታ ጥራት አግባብ በያዝነው ዓመት ቀሪ ወራት ሲጠናቀቅ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ዋጋን በዘላቂነት ለማረጋጋት ያስችላል ያሉት አሕመዲን መሐመድ(ዶ/ር) የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆንም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026