አዲስ አበባ ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ)፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የስራ እንቅስቃሴን ዛሬ ጎብኝተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ኮሚሽኑ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ምህዳር በእጅጉ ያሻሻሉ የሪፎርም ተግባራትን ማከናወኑን አይተናል ሲሉ አስፍረዋል።
ተቋሙ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እና ዘመናዊ የዲጂታል አሰራሮችን የተከተለ የደንበኞች አገልግሎት አሰራርን ተግባራዊ አድርጎ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለዘርፉ ትልቅ ዕድል የከፈተ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ የተገኘው ስኬትም ይህንኑ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በቀጣይ ኮሚሽኑ የጀመረውን አበረታች እና ከኢኮኖሚ ዕቅዶቻችን ጋር የተጣጣመ ዒላማ ተኮር የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጠናል ሲሉም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025