የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አፍሪካ በዌልዲንግ ዘርፍ ያላትን ትልቅ አቅም ለመጠቀም የሀገራት የጋራ ስራ ሊጠናከር ይገባል

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፡-አፍሪካ በዌልዲንግ ዘርፍ ያላትን ትልቅ አቅም ለመጠቀም የሀገራት የጋራ ስራ ሊጠናከር እንደሚገባ የፌዴራል ቴክኒክ ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡

ከሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ዓመታዊ ጉባኤና ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።


በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አቡደል አሊም፣የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

የፌዴራል ቴክኒክ ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፥ ጉባኤው ስኬታማ ነበር።

በጉባኤው ለዌልዲንግ ዘርፍ ስኬታማነት አስተዋፅኦ የሚያደርጉ ፍሬያማ ውይይቶች የተደረጉበት እንዲሁም አፍሪካ በብየዳ ሙያ ያላትን ትልቅ አቅም ያሳየችበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የአፍሪካ ሀገራት ትስስራቸውን በማጠናከር ዘርፉን በጋራ ለማሳደግ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ነው ብለዋል።


የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አቡደል አሊም፥ ኢትዮጵያ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ሰጥታ ጉባኤውን በተደራጀ ሁኔታ በማዘጋጀቷ ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

ጉባኤው በአህጉሪቱ ስላለው የዌልዲንግ አቅም ግንዛቤ የተፈጠረበት፣ ዘርፉን ለማጠናከር ትምህርት የተገኘበትና በጋራ መስራት እንደሚገባ መግባባት የተደረሰበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡

በጉባኤው አፍሪካውያን የዌልዲንግ ልምዳቸውን የተለዋወጡበትና በዘርፉ ተጨማሪ እውቀት የቀሰሙበት መሆኑን የተናገረችው በጉባኤው የተሳተፈችው ደቡብ አፍሪካዊቷ ኮንፊዲ ሎኮንዴ ናት፡፡


ጉባኤው የዌልዲንግ ባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ በኩል ወሳኝ እንደነበር በማንሳት፥ ኩባንያዎች በዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን ፈሰስ በማድረግ ለዘርፉ ዕድገት እንዲሰሩም ጠይቃለች።

በጉባኤው በተካሄዱ ውድድሮች ያሸነፉ ግለሰቦች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፥ አራተኛውን የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ጉባኤ ደቡብ አፍሪካ እንደምታስተናግድ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026