የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ።


የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ኃላፊው አቶ እንድሪስ አህመድ ገልጸዋል።

በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ኤር ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ወደ ጋዝ ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ብሬከር የመቀየር ሥራ መሰራቱ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የብሬከር ቅየራው አሁን ላይ 70 በመቶ መድረሱንና ሲጠናቀቅ የጣቢያውን ኃይል የማቅረብ አቅም አስተማማኝና የተቀላጠፈ እንደሚያደርገውም መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመላክታል።


የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ለሰመራ፣ ለሎጊያ፣ ለሚሌ፣ ለአሳይታ፣ ለዱብቲ ከተሞችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ያስችላል ያሉት ደግሞ የሪጅኑ ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ አብዱ ናቸው።

የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል ብለዋል።

አንድ ገቢ መስመርና ሁለት ወጪ መስመሮች ያሉት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ በ2003 ዓ.ም ተገንብቶ ለክልሉ በዋነኛነት ኃይል በማቅረብ እያገለገለ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026