የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮችን ማነቆ በመፍታት ውጤታማነታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ ነው-ሚኒስቴሩ

Apr 14, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ሚያዝያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ማነቆዎች በመፍታት ውጤታማነታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማና የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ተካሄዷል።

በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሐመድ እንዳሉት፥ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ግብርናን ከማዘመን ባለፈ ወደ ኢንዱስትሪ ለሚደረገው ሽግግር መሰረት ናቸው።


በሀገሪቱ የሚገኙ እነዚህ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች ምርቶች ላይ እሴት ጨምረው የማቀነባበር ሚናቸውን እንዲወጡና ውጤታማነታቸውን ለማረጋገጥ የሚገጥማቸውን ማነቆዎች መፍታትን ጨምሮ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርኮቹ በተለይም የፋይናንስ፣ የኃይል አቅርቦትና የገበያ ትስስር ችግሮች መለየታቸውን ገልጸው፥ በተቀናጀ መንገድ በመፍታት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዲላና የይርጋጨፌ መካከለኛ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮችን በማስተዋወቅ አልሚ ባለሃብቱን በመሳቡ ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ ናቸው።


ፓርኮቹ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተከናውኖላቸው ለምርት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በተለይ የዲላው ፓርክ የአቮካዶ ዘይት በማምረት በወጪ ንግድና በስራ ፈጠራ ረገድ ውጤታማ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

በቀጣይ 90 ቀናት ወደ ፓርኩ ለመግባት ፍላጎት ያሳዩ 6 ባለሃብቶችን ስራ በማስጀመር የፓርኩን ውጤታማነት ለማጠናከር ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጸዋል።

በመድረኩም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026