
ዲላ፤ሚያዝያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ማነቆዎች በመፍታት ውጤታማነታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማና የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሐመድ እንዳሉት፥ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ግብርናን ከማዘመን ባለፈ ወደ ኢንዱስትሪ ለሚደረገው ሽግግር መሰረት ናቸው።

በሀገሪቱ የሚገኙ እነዚህ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች ምርቶች ላይ እሴት ጨምረው የማቀነባበር ሚናቸውን እንዲወጡና ውጤታማነታቸውን ለማረጋገጥ የሚገጥማቸውን ማነቆዎች መፍታትን ጨምሮ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፓርኮቹ በተለይም የፋይናንስ፣ የኃይል አቅርቦትና የገበያ ትስስር ችግሮች መለየታቸውን ገልጸው፥ በተቀናጀ መንገድ በመፍታት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዲላና የይርጋጨፌ መካከለኛ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮችን በማስተዋወቅ አልሚ ባለሃብቱን በመሳቡ ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ ናቸው።

ፓርኮቹ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተከናውኖላቸው ለምርት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በተለይ የዲላው ፓርክ የአቮካዶ ዘይት በማምረት በወጪ ንግድና በስራ ፈጠራ ረገድ ውጤታማ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።
በቀጣይ 90 ቀናት ወደ ፓርኩ ለመግባት ፍላጎት ያሳዩ 6 ባለሃብቶችን ስራ በማስጀመር የፓርኩን ውጤታማነት ለማጠናከር ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጸዋል።
በመድረኩም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026