የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017( ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በበጋ መስኖ በመጀመሪያው ዙር ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱ ተገለፀ።

በበጋ መስኖ ልማቱ ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የመስኖ ልማት ዳይሬክቶሬት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀየሎም ተካ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በመጀመሪያው ዙር በመስኖ ከለማው 58 ሺህ ሄክታር መሬት የ54 ሺህ ሄክታሩ የምርት ግምገማ ተጠናቋል።

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት አስካሁን በተሰበሰበው መረጃ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።

በበጋ መስኖ የለማው አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎች እንደሚገኙባቸው የገለፁት አስተባባሪው ሁለተኛው ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።


የአርሶ አደሩ የመስኖ ልማት ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት አስተባባሪው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራታቸው፣ የግብዓት አቅርቦትና የባለሙያ ድጋፍ ታክሎበት የተሻለ ምርት ሊገኝ መቻሉን ገልፀዋል።

በዘንድሮው የመጀመሪያ ዙር የመስኖ ልማት ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀው ከዚህም ውስጥ 39 ሺህ 506ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመስኖ ልማት የተሳተፉ አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ሌሎች አርሶ አደሮችን ለተሳትፎ ማነሳሳቱንም አስተባባሪው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026