የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ ይሻል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ/ ቦንጋ/ አርባምንጭ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን በተለያዩ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከባህር በቅርብ ርቀት ላይ ሆና የባህር በር ተነፍጓት ብትቆይም አሁን ላይ የሀገር የህልውና ጉዳይ እና የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ መነሳት ከጀመረ ውሎ አድሯል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ተደጋጋሚ ማብራሪያዎችን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የበዛ ህዝብ ይዘን ተቆልፎብን መኖር ስለማንችል የባህር በር ጉዳይ የህልውና ጥያቄ መሆኑን በተደጋጋሚ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው ላይም የባህር በር ጉዳይ ምላሽ የሚሻ የትውልዱ ጥያቄ መሆኑን ማስፈራቸው ይታወቃል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በአዳማ፣ ቦንጋ እና አርባ ምንጭ ከተሞች ያነጋገራቸው ወጣቶች የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን ተናግረዋል።


የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው ወጣት ተገኝ አበራ፣ የቦንጋ ከተማ ነዋሪው ወጣት አክሊሉ ሀይለማሪም እና የአዳማ ከተማ ነዋሪው ወጣት አቤሜሌክ አየለ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ ለሀገር የህልውና መሰረት ከመሆኑም በላይ የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ እንደሚሻ ገልጸዋል።


በዚህ ረገድ መንግስት ጥያቄውን አንስቶ ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ አጠናክሮ መቀጠሉን በማድነቅ ለስኬታማነቱ የድርሻችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎቹ ወጣት ግሩምነሽ ሀጫ እና ወጣት ቀኝያለው ትዕዛዙ፤ የባህር በር ጥያቄው በሰጥቶ መቀበል መርህ በመንግስት የተጀመረው የዲፕሎማሲ ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ በመደመር መርህ ብሔራዊ ጥቅምን፣ ሀገራዊ ልማትና እድገትን አንግቦ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ወጣቶቹ ቀጣይነት ያለው ጥረት እናደርጋለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊነትን ያነገበና የሀገር የህልውና ጉዳይ በመሆኑ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026