የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የማዕድን ልማት አሰራሮችን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እያደገ ነው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የማዕድን ልማት አሰራሮችን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እያደገ መምጣቱን የክልሉ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ገለጸ።

ከክልሉ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ወራት የተለያየ የማዕድናትን በብሔራዊ ባንክ በኩል ለውጪ ገበያ በማቅረብ 605 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

በተጨማሪም ለአገር ውስጥ ገበያ ከቀረበ የማዕድን ምርት ከ1 ቢሊየን 600 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ባለሥልጣኑ አስታውቋል።

የኦሮሚያ ክልል ማዕድን ልማት ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ለሜሳ ለኢዜአ እንደተናገሩት ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ከዘርፉ ትልቅ ጥቅም እየተገኘ ነው።

በዚህም የማዕድን ዘርፉ በአግባቡ እንዲመራ ለማድረግ ደንቦች፣ ህጎችና መመሪያዎች ተዘጋጅተው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በተደረጉ ማሻሻያዎች ከማዕድን ሀብቱ ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ገልጸው ከዘርፉ የሚገኘው ገቢም እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥ ገበያ ከቀረበው የማዕድን ምርት 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እስከ አሁን 1 ቢሊየን 600 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ነው የገለጹት።

በክልሉ የማዕድን ልማት ዘርፍ የውጭ ምንዛሪ ከማስገኘት ባለፈ ለበርካታ ዜጎችም የስራ እድል እየፈጠረ መምጣቱንም አስረድተዋል።


በባለስልጣኑ የጂኦሎጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ አለማየሁ ኦልጂራ በበኩላቸው በክልሉ የተለያዩ ማዕድናት የሚገኙበትን ቦታ ለመለየት ብዙ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በክልሉ እስከ አሁን ለኢንዱስትሪ ግብዓት፤ ለጌጣጌጥ እና ብረታብረት ምርት የሚውሉ 76 አይነት ማዕድናት መለየታቸውን ገልጸዋል።

ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹን ወደ ምርት በማስገባት ለኢንዱስትሪ ግብዓት እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026