
ደሴ፣መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡ -እየጣለ ያለው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ምቹ በመሆኑ አርሶ አደሩ የሰብል ልማቱን ማቀላጠፍ እንዳለበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አሳሰበ፡፡
የማዕከሉ የልማት ሚቲዎሮሎጂ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳላማው ወልዴ ለኢዜአ እንደገለጹት የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ፈጥነው ለሚደርሱ ሰብሎች ምቹ ነው።
አርሶ አደሩ በምስራቅ አማራ ዞኖች የሚዘንበውን ቀላልና መካከለኛ ዝናብ ተጠቅሞ ፈጥነው መድረስ የሚችሉ ሰብሎች ላይ በማተኮር የዘር ስራውን ማቀላጠፍ እንዳለበት ገልጸዋል።
ከዚህ ጎን ለጎንም የሚዘንበውን ዝናብ በማሳ ዳር ዳር አቅቦ በማስቀረትና ወደ ግድቦችና ኩሬዎች በማስገባት የዘሩት ሰብል ምርታማ እንዲሆን አልመው መስራት እንደለባቸው አሳስበዋል።
የበልግ ዝናቡ ለሰብል ልማት፣ ለእንሰሳት ግጦሽ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማትም የሚያስገኘው ጠቀሜታ ከፍ ያለ በመሆኑ በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
የበልግ ዝናቡ ደረቅና ሞቃት የአየር ጸባይ ስለሚፈጥር ህብረተሰቡ ከተለያዩ በሽታዎች እራሱን እንዲጠብቅ ያሳሰቡት አቶ እንዳላማው በተለይ የወባ መራቢያ ሥፍራዎችን ማጽዳት ይኖርበታል ብለዋል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው በዞኑ የበልግ ዝናብን በመጠቀም ከ50 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በተለያየ የሰብል ዘር ተሸፍኗል ብለዋል፡፡
አርሶ አደሩ ያገኘውን እርጥበት ተጠቅሞ ወደ ልማቱ እንዲገባ በየደረጃው ባሉ የግብርና ባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
በዞኑ ከ104 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ በማልማት ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026