የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአዳማ ከተማ የካዳስተር የመሬት አስተዳደር ስርዓት በጥሩ ተሞክሮነት የሚወሰድ ነው

Apr 8, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ) ፡-የአዳማ ከተማ የካዳስተር የመሬት አስተዳደር ስርዓት በጥሩ ተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑ ተገለጸ።

በአዳማ ከተማ 117 ሺህ የመሬት ይዞታ ፋይሎች ወደ ካዳስተር እንዲገቡ መደረጉን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና መሬት ቢሮ የተወጣጣ ቡድን የአዳማ ከተማን የመሬት አስተዳደር የዲጂታል አሰራርና ካዳስተር አገልግሎት በተመለከተ ልምድ ተጋርቷል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ ዝናቡ ተካበ፤ በአዳማ ከተማ የመሬት ሀብት አስተዳደርና አገልግሎቶች አሰጣጥ ዘመኑን የዋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይ የመሬት ሀብቱን በአግባቡ ለማስተዳደርና ለመጠቀም የተጀመረው የካዳስተር ስራ የሚደነቅና በጥሩ ተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ተናግረዋል።

ከአዳማ ቆይታቸው በአገልገሎት አሰጣጥ የመሬት ማኔጅመንትና ተያያዥ ጉዳዮችን በመጎብኘት ጠቃሚ ልምዶችና አሰራሮችን በመቅሰም በከተሞቻቸው ለመተግበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ፤ በከተማዋ የመሬት ሀብትን በአግባቡ ለማስተዳደር፣ ለማልማትና ለመጠቀም የዲጂታል አገልግሎት ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።


በካዳስተር አሰራር ከሊዝ አዋጅ በፊት የተገነቡ ሰነድ አልባ ቤቶች ወደ ህጋዊ ስርአት እዲገቡ እንዲሁም 117 ሺህ የመሬት ይዞታ ፋይሎች ወደ ካዳስተር እንዲገቡ መደረጉንም ተናግረዋል።

በህገ ወጥ መንገድ ተይዞ የነበረ በድምሩ ከ200 ሄክታር በላይ መሬት ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ መደረጉን ጠቅሰው ግልጽ አሰራርና ተጠያቂነትን በማስፈን የዘርፉን ገቢ ከማሳደግ ባለፈ ብልሹ አሰራርን መከላከል መቻሉን ጠቅሰዋል።

ከሊዝ አዋጅ በፊት የነበሩ ሰነድ አልባ ይዞታዎችን ወደ ህጋዊ መስመር ለማስገባት የተደረገው ጥረት ስኬታማ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ሂደት አሰራሩን ህጋዊ ከማድረግም ባለፈ ከ610 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026