የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ትልቅ ድል ያስመዘገበበት ነው- የግብርና ሚኒስቴር

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ትልቅ ድል ያስመዘገበበት መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።

የግብርና ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኖች ባለፉት 7 ዓመታት በለውጡ መንግስት በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ስኬቶች ላይ ‘ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!’ በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት አካሂደዋል፡፡

የሚኒስቴሩ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፈ ሚኒስትር ዴኤታ እያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ባለፉት ሰባት የለውጥ አመታት እንደ ሀገር በርካታ ውጤቶችና ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል

ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ ላይ የተጋረጠውን የመበታተን አደጋና ስጋት ተቀርፎ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የተደረገበት ቀን እንደነበር አውስተዋል።


ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘውም በለውጥ ዓመታቱ የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ትልቅ ድል የተመዘገበበት ነው ብለዋል።

በስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራና በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮች የተመዘገቡ ውጤቶች የምግብ ዋስትናን እና ስርዓተ ምግብ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርና ለመገንባት በሚደረገው ጥረት መሰረት የተጣለበት እንደሆነ አመልክተዋል።

የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት የለውጡ አመታት በኢኮኖሚው ዘርፍ በግብርና ላይ ብቻ የተንጠለጠለውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ለማድረግ ከግብርናው ባለፈ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝምና በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ዘርፎች ላይ ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል።

በግብርናው ዘርፍ የመጣው ለውጥ የሚታወስና ብዙ የታሪክ እጥፋቶች የመጣበት መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸው የተገኘውን ድል ለማጽናትና ለማስቀጠል አመራሩና ሰራተኛው በበለጠ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አሳስበዋል።

በለውጡ ዓመታት የተገኙ ድሎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም አጠቃላይ በኢኮኖሚውና በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት እንደተደረገበት የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026